ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዘመነ ክረምት የሕጻናት ት/ት መርሐግብር

እንኳን ወደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ልዩ የዘመነ ክረምት የሕጻናት ት/ት መርሐግብር በደኅና መጡ። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዘመነ ክረምት የሕጻናት ት/ት መርሐግብር ዕድሜያቸው ከ7 እስከ 14 ዓመት ለሆኑ ሕጻናት በአዳር እንዲሁም በተመላላሽ የት/ት ማዕቀፍ ለ6 ሳምንታት የሚሰጥ ስልጠና ነው።

300+

ያገለገልናቸው ተማሪዎች

4+

የስልጠናው ዙሮች

200+

አገልጋዮች

በሃምረ ብርሃን የሚማሩ ህፃናት
ሰለ ስልጠናው

የት/ት መርሐግብሩ የትኩረት አቅጣጫዎች.

የት/ት መርሐግብሩ በዋናነት ትኩረት አድርጎ የሚሰራው ልጆች እግዚአብሔርን የሚፈሩ፣ ሰውን የሚያፍሩ፣ በጥምቀት የተወለዱባትን ቅድስት ቤ/ክ ሥርዓት እና ሕግ በፍቅር የሚጠነቅቁ እና የሚያገለግሉ፣ ያሳደጋቸውን ቤተሰብ እና ማኅበረሰብ በጎ ዕሴቶች የሚጠብቁ በአጠቃላይ መንፈሳዊ ተግባራትን በዘላቂነት እንዲተገብሩ ለማስቻል የሚሰራ ሲሆን የት/ት መርሐግብሩ በተሰጠባቸው ያለፉት 4 ዙሮች በእግዚአብሔር እና በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ረዳትነት ከላይ የተጠቀሱት ሀሳቦች በልጆች ሕይወት ላይ እንዲንጸባረቁ እና ፍሬ እንዲያፈሩ እየተሰራ ይገኛል።

በቆይታቸው ልጆች መሠረታዊ የቤ/ክ ት/ቶችን፣ የአብነት ት/ትን የሚማሩ ሲሆን የሥዕል የሐረግ ጥበብ እና ሌሎች የተግባረ እድ ስልጠናዎችንም ይወስዳሉ። ከእነዚህም በተጨማሪ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው የጎለመሱ በሕይወት ክህሎት የጠነከሩ ይሆን ዘንድ ስልታዊ የማስተማሪያ ዘዴዎችን እና የተለያዩ መርሐግብራት በመቅረጽ የተማሯቸውን ትምህርቶች ተግባራዊ በሆነ መንገድ እንዲረዷቸው እና ወደ ሕይወታቸው አምጥተው እንዲጠቀሙባቸው ትኩረት ተደርጎ ይሰራል።

ልጆች ፍቅረ ቤ/ክን እና መዓዛ ቤ/ክ በልቡናቸው ውስጥ የበለጠ ያድር ዘንድ በዕለተ ሰንበት ጉዞዎችን በማዘጋጀት አቅራቢያ ያሉ ገዳማትን  አድባራትን እንዲሳለሙ የሚደረግ ሲሆን በት/ት መርሐግብሩ ማጠቃለያም ዐቢይ ጉዞ በማዘጋጀት ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቤ/ክ ገዳማትን እና ቅዱሳን መካናትን እንዲጎበኙ ይደረጋል።

የመጀመሪያ ዓመት (2013ዓ.ም)

ቦታ: አዲስ አበባ ፒያሳ | ቆይታ: 2 ወር

7

ተማሪዎች

0

ተመላላሽ

10+

አገልጋዮች

ሁለተኛ ዓመት (2014ዓ.ም)

ቦታ: አዲስ አበባ ፒያሳ | ቆይታ: 2 ወር

17

ተማሪዎች

5

ተመላላሽ

12+

አገልጋዮች

ሦስተኛ ዓመት (2015ዓ.ም)

ቦታ: አዲስ አበባ | ቆይታ: 2 ወር

80

ተማሪዎች

0

ተመላላሽ

50+

አገልጋዮች

አራተኛ ዓመት (2016ዓ.ም)

ቦታ: አዲስ አበባ | ቆይታ: 2 ወር

154

ተማሪዎች

120

ተመላላሽ

100+

አገልጋዮች

ዘንድሮ አምስተኛ ዓመት (2017ዓ.ም)

ቦታ: አዲስ አበባ | ቆይታ: 6 ሳምንት

250

ተማሪዎች

300

ተመላላሽ

200+

አገልጋዮች

የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አርማ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ልጅዎን እኛ ጋር
ለምን ያስተምራሉ?

01.

እውቀት ብቻ ሳይሆን ሕይወትንም ይማራሉ

መንፈሳዊ ት/ቶችን መማር ብቻ ሳይሆን የተማሯቸውን ትምህርቶች እንዴት በሕይወት መኖር እንዳለባቸው መንገድ የሚያሳዩ መንፈሳዊ የሕይወት ልምምዶችንም ያደርጋሉ።

02.

መሠረታዊ የሆኑ የሕይወት ክህሎቶችን ያዳብራሉ

ራስን ችሎ ነገሮችን የመከወን፣ ማንኛውንም አይነት ቦታ እና ሁኔታን ተላምዶ እና ተቋቁሞ የመኖር ክህሎቶችን ያሳድጋሉ።

03.

አገልጋይ መሆንን ይማራሉ

እነርሱን ለማገልገል ዋጋ የሚከፍሉ አገልጋዮችን እና እነርሱን ለመጎብኘት ዋጋ ከፍለው የሚመጡ የክብር እንግዶችን፣ ሊቃውንት መምህራንን እና ትልልቅ አባቶችን እና እናቶችን በማየት አሁን ባላቸው አውም ቤ/ክንን ለማገልገል ራሳቸውን ዝግጁ ያደርጋሉ ነገ አድገው ለቅድስት ቤ/ክ ደርሰውላት በብዙ አቅም ለማገልገል ይዘጋጃሉ።

04.

መሠረታዊ እውቀቶችን ያገኛሉ

መሠረታዊ የቤ/ክ ትምህርቶች ላይ፣ የአብነት ት/ት ላይ እና የተግባረ እድ ትምህርቶች ላይ ስልታዊ የሆኑ የማስተማሪያ ዘዴዎችን በመጠቀም መሠረታዊ እውቀቶች እንዲኖሯቸው ይሠራል።

የሃምረ ብርሃን ተሳታፊ 1የሃምረ ብርሃን ተሳታፊ 2የሃምረ ብርሃን ተሳታፊ 3የሃምረ ብርሃን ተሳታፊ 4

ልጆቻችንን ለመቀበል ዝግጁ ነን!!  

ስለ ት/ት መርሐግብሩ የተሰጡ ምስክርነቶች

ልጅን አሳልፎ ለእግዚአብሔር ሰጥቶስ ነገ እኛም መልሰን የምንባረክበት ቦታ እኔ በሕይወቴ በዘመኔ በዚህ እድሜዬ ስላገኘሁ ደስተኛ ነኝ።

የየተማሪ ወላጅ አቶ ነጻነት ዘነበ ፎቶ

አቶ ነጻነት ዘነበ

የተማሪ ወላጅ

የመጀመሪያ ቀን እንደ እናት በጣም አልቅሻለሁ በተለይ የመጨረሻ ልጄ 7 ዓመቱ ነውና እንደ እናት ይከብዳል ግን ዓላማ ነው።

የወላጅ ወ/ሮ ኪያ ፎቶ

ወ/ሮ ኪያ

ወላጅ

ቤ/ክንን የተረዳ ክርስቶስን የሚያገለግል ለክርስቶስ ራሱን የሚሰጥ ራሱን የሚሰዋ ቅዱስ ንጹሕ የሆነ መስዋዕት አድርጎ ራሱን ለእግዚአብሔር የሚያቀርብ ትውልድ ማየት እናፍቃለሁ።

የመምህር መምህር አብርሃም ፎቶ

መምህር አብርሃም

መምህር

ካህናቱ ጳጳሳቱ ዲያቆናቱ ተወልደዋል ጥያቄው እንዴት እያደጉ ነው? ማን እያሳደጋቸው ነው? የሚለው ነው።

የመምህር እና የስነ ልቡና ምሁር መምህር ሳምሶን ወርቁ ፎቶ

መምህር ሳምሶን ወርቁ

መምህር እና የስነ ልቡና ምሁር

እኛ በራሳችን የምንጥራቸው ጥረቶች የተወሰነ ተጽዕኖ ቢኖረውም እዚህ ግን ፍጹም ከእኛ ማግኘት የማይችሏቸውን ነገሮች ነው ያገኙት።

የወላጅ አቶ ሳምሶን ፎቶ

አቶ ሳምሶን

ወላጅ

በ15ተኛው ቀን ልጆቼን ለማየት ስመጣ ልጆቼ ዝቅ ብለው ሰላም ላንቺ ይሁን ብለው ጉልበቴን ሲስሙኝ በጣም ደነገጥኩኝ ምን አይነት ት/ት ቤት ነው ልጆቼን ያስገባሁት አልኩኝ።

የወላጅ ወ/ሮ ስንዱ ፎቶ

ወ/ሮ ስንዱ

ወላጅ

በጣም ትሕትናን መታዘዝን ቤት ውስጥ ሐሙስ አስቦ የእኛን እግር የማጠብ ልምድን ይዘው ወተዋል።

የወላጅ ወ/ሮ ገነት ፎቶ

ወ/ሮ ገነት

ወላጅ

ሁሉም ሰው ወንድም እና እህቴ ነው።

የተማሪ ካሌብ ሰሎሞን ፎቶ

ካሌብ ሰሎሞን

ተማሪ

ሐመረ ብርሃን በጣም ብዙ ደስ የሚሉ ነገሮች አሉ ሥዕል በገና ውዳሴ ማርያም ጠዋት ስንክሳር ሲነበብልን ጸሎቱ እግር አጠባው ዝክር ስንዘክር ዳቦ ስንጋግር የብራና ላይ ጽሑፉ ት/ቱ ሁሉ ነገር ደስ ይላል።

የተማሪ ጋብሬላ ዮናታን ፎቶ

ጋብሬላ ዮናታን

ተማሪ