ሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ
ሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ተቋም "ንግባእኬ ኀበ ጥንተ ነገር" "ወደ ቀድሞው ነገር እንመለስ" በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክንን ጥንታዊ እውቀት እና ጥበብ፣ የቅድስት ቤ/ክንን ትውፊት እና አስተምህሮ የጠበቁ ኦርቶዶክሳዊ የተግባረ እድ ውጤቶችን ለመስራት እና ለተተኪው ትውልድ ለማስተላለፍ በ2011ዓ.ም በመሀል አዲስ አበባ ፒያሳ ላይ ሥራውን ጀመረ።
በዚህም ስራው ላለፉት 6 ዓመታት በ7 ዘርፎች፣ በ5 ቅርጫፎች፣ ከ80+ በሚሆኑ መደበኛ ሠራተኞች እና ከ400+ በሆኑ በጎ ፈቃደኛ አገልጋዮች ዓላማውን ለማስፈጸም እየሠራ ሲሆን ከእነዚህ ዘርፎችም አንዱ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የሕጻናት ት/ት መርሐግብርን፣ ለወጣቶች የሚሰጡ የተግባረ እድ ስልጠናዎችን እና ሌሎች ሰፋፊ አገልግሎቶችን እየሰጠ የሚገኘው የት/ት እና ስልጠና ክፍል ከሰባቱ ዘርፎች አንዱ ነው።
ስለ ሐመረ ብርሃን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ድኅረ ገጻችንን ይጎብኙ።
ሐመረ ብርሃን የሚሠራቸውን፣ ጊዜያዊ ሳይሆኑ ታሪካዊ የሆኑና ለትውልድ የሚተላለፉ ድንቅ ሥራዎችን አሁን ያለው ትውልድ እንዲያውቃቸውና የሙያ ባለቤትም በመሆን የዚህ ጥበብ ማዕድ ተካፋይ እንዲሆኑ የተለያዩ ትምህርቶችን እና ስልጠናዎችን እየሠጠ ይገኛል። የሚሰጡት ት/ት እና ስልጠናዎችም የቀደምት አባቶቻችንን ጥንታዊ ጥበባት እና እውቀቶችን አሁን ያለው ትውልድ እንዲያያቸው እና እንዲያውቃቸው፣ ለሥራዎችቻቸውም ያለው ክብር እንዲያድግ፣ በዚህ ዘመን ትውልድ እና በቀደምት አባቶች መካከል ያለው የጥበብ ሰንሰለት ሳይበረዝ እንዲቀጥል እና ትውልዱ የአባቶቹን ሥራ ተመልክቶ ከመደነቅ ባለፈ የሚከውን እንዲሆን የሚያደርጉ ናቸው። ትምህርት እና ስልጠና ክፍሉ ወጣቶች ላይ እንዲሁም የዚህ ሥራ ዋና ተረካቢ እና አስቀጥይ የሆኑ ሕጻናት ላይ እየሠራ የሚገኝ ሲሆን
እስካሁን በስልጠና ጊዜ ውስጥ
የሐመረ ብርሃን ማኅበራዊ ድኅረ ገጾች
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዘመነ ክረምት መርሐግብር ከ7 እስከ 14 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ ላሉ ህፃናት የተዘጋጀ የክረምት ካምፕ (Summer Camp) ነው። መርሐግብሩ ልጆች እንደፍላጎታቸው በአዳሪነት ወይም በተመላላሽነት እንዲሳተፉ እድል ይሰጣል።
ልጆቻችንን ለመቀበል ዝግጁ ሁነን እየጠበቅን ነው።
ቦታ ለማስያዝ ይህን ይጫኑ